Kód: 52746830
የኢትዮጵያ እና የካናዳ አሳዳጆች፤በዓለም አቀፍ ደረጃ አዲስ ነገር ይዞ የመጣው መጽሐፍ፤ ምንስ አዲስ ነገር አለው?ያለወትሮው ብርዳማ የነበረው የቶሮንቶ ሰማይ፣ ዛሬ ደስ የሚል የፀሐይ ብርሃን ተተክቷል። ከተማዋ ፈገግ ብላለች፤ ነዋሪዎቿም በሰላማዊው ድባብ ተመስጠዋል። ነገር ግን ከዚህ ደማቅ ብርሃን በስተጀርባ፣ በከተማዋ ላይ የሚሰነዘር ከባድና አውዳሚ ሴራ እየተ ... celý popis
Afrikánčina
30.98 €
Bežne: 34.39 €
Ušetríte 3.41 €

Nákupom získate 75 bodov
Anotácia knihy
የኢትዮጵያ እና የካናዳ አሳዳጆች፤
በዓለም አቀፍ ደረጃ አዲስ ነገር ይዞ የመጣው መጽሐፍ፤ ምንስ አዲስ ነገር አለው?
ያለወትሮው ብርዳማ የነበረው የቶሮንቶ ሰማይ፣ ዛሬ ደስ የሚል የፀሐይ ብርሃን ተተክቷል። ከተማዋ ፈገግ ብላለች፤ ነዋሪዎቿም በሰላማዊው ድባብ ተመስጠዋል። ነገር ግን ከዚህ ደማቅ ብርሃን በስተጀርባ፣ በከተማዋ ላይ የሚሰነዘር ከባድና አውዳሚ ሴራ እየተዶለተ ነው። መላ ነዋሪዎችንና ኢትዮጵያውያንንም ሊጠልፍ እየተሰናዳ ነው፡፡
ቶሮንቶ ወደ ምስቅልቅል ትርምስ ለመግባት ደቂቃዎች ብቻ ቀርተዋታል። ይህንን አስከፊ ሴራ ግን ያቺ ብሩህ ፀሐይም ሆነች የፈገግታ ጭንብል የለበሰችው ከተማ ቅንጣት ያህል አያውቁም። መንግሥት፣ የደህንነት ተቋማትና ነዋሪዎች ከተማዋ ላይ ባለው በሰላማዊው ድባብ ተታለዋል። ከተማዋ ከበረዶ ሸሽታ በፀሐይ ስትደምቅ፣ ሳታውቀው በጉያዋ የታቀፈችው ጥፋት በድንገት በእሳት ብልጭታ ሊሞላት ነው!
ይህ ድንገተኛ አደጋ ባልታሰበ መንገድ ተጉዞ ከኢትዮጵያዊቷ ሕይወት ጋር እንዴት ሊተሳሰር ቻለ? እሷንስ በሴራው ወጥመድ ውስጥ ይጠልፋት ይሆን? ወይስ ሌላ የማይታሰብ ክስተት ይፈጠር ይሆን?
. . .
የመርማሪው ሄርሞን የመጨረሻ ተስፋ ሰላማዊ ዕረፍት ነበር-ነገር ግን ያገኘው ሳያስበው ሊገባ የደረሰው የሞት አፋፍ ላይ የሚያደርስ የሴራ ማዕበል ነው! በአሁኑ ሰዓት ግን እሱ ይሄንን አያውቅም። የሚያውቀው ነገር ቢኖር ላለፉት ዓመታት ያለ ዕረፍት ሲሠራ እንደነበር እና ዛሬ ስልኩን ዘግቶ ለሦስት ሳምንታት የሚቆይ የዓመት ዕረፍቱን በቶሮንቶው ሃይ ፓርክ (High Park) እንደጀመረ ብቻ ነው።
ነገር ግን በዛፎቹ ጥላ ስር የነበረው ጸጥታ በድንገት ተሰበረ። የሰማው ምስጢራዊ "ኮድ" ሁሉንም ነገር ቀየረው። ይህ ንግግርና ኮድ ለራሱም ወደ ሞት የሚወስደው፣ ለከተማዋም ውድቀትና መተራመስ ምክንያት የሚሆን ነው። ኢትዮጵያዊቷንም በስበት አውዳሚ ችግር ውስጥ የሚከት፣ በተጨማሪም አጠቃላይ የከተማ ነዋሪውንም ሆነ ከተማዋን ከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ የሚከት ነው። ሰላምና ዕረፍት ፈልጎ የወጣው ሄርሞን፣ ባልታሰበ ሁኔታ በተለያዩ እሳቶች መሃል ወደቀ፦
የጊዜ ሩጫ፦
Parametre knihy
30.98 €
AfrikánčinaOsobný odber Bratislava a 12792 dalších
Copyright ©2008-26 najlacnejsie-knihy.sk Všetky práva vyhradenéSúkromieCookies
24 miliónov titulov
Vrátenie do mesiaca
02/210 210 99 (8-15.30h)Nákupný košík ( prázdny )
Nachádzate sa: